በሳውላ ፖሊቴክኒክ ተመርቶ ፤ለሳውላ ከተማ ውበት የዋለ!
ከተማችን ሳውላ በኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ውብ የእግረኛ መንገድ እና የጎዳና ላይ መብራቶች ተገጥመውላት ይበልጥ እየተዋበች ትገኛለች። የእኛ ሳውላ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለዚህ ታላቅ የከተማዋ ልማት ቀጥተኛ አስተዋጽኦ በማድረጉ ትልቅ ኩራት ይሰማዋል። በኮሌጃችን ቴክኒካል ቡድን እና አሰልጣኞች ጥራታቸውን ጠብቀው የተመረቱት የኮሪደር የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች (poles) በአሁኑ ወቅት የከተማችንን መንገድ እያደመቁ ይገኛሉ።
ይህ ስኬት ኮሌጃችን የተግባር ስልጠናን፣ የኢንጂነሪንግ ብቃትን እና ከማህበረሰቡ ጎን መቆምን በተግባር ያረጋገጠበት ነው። እኛ ቴክኖሎጂን ማስተማር ብቻ ሳይሆን ከተማችንንም እንገነባለን!
አብረን ለሳውላ ብሩህ ተስፋ እንገነባለን!
#SawlaPolytechnic #CorridorDevelopment #SawlaCity #VocationalExcellence #CommunityImpact